| ለምትሰሩት ስህተት ሁሉ ህዝቡ ምን ይላችሁ መሰላችሁ? |
|
|
| Friday, 05 October 2007 | |
|
በቅንጅት ስም ለምትሰሩት ስህተት ሁሉ ህዝቡ ምን ይላችሁ መሰላችሁ? አደብ ግዙና ጠላት መሳቂያ ሳያደርገን ቆም ብላችሁ አስተውሉ ፤ ሰድባችሁ ለሰዳቢ አትስጡን ፤ ስጋችሁን በጎመን አትለውጡ
ሳተናው ቀበሮ ከአዲስ አበባ
በቅርቡ ጆሮ አልሰማው አይል የሆነበት በግንቦቱ ምርጫ የመረጥናቸው አመራሮቻችን በግፍ ከታሰሩበት ወህኒ እግረ ሙቁ ወልቆላቸው ከእስር እንዲወጡ ብርቱ ትግል ያደረገውን በውጭ ነዋሪ ወገንና የውጪ ተወላጆችን ለማመስገን ባህር ማዶ ከሄዱ በሁዋላ በመካከላቸው ተፈጠረ እየተባለ ስለሚራገበው ወሬና እንዲህም እንዲሆን መንገዱን ላሳዩ፤ ላመላከቱ ስለሆነው ሁሉ እኔ ጸሃፊው ቅር ስለተሰኘሁባቸው አንዳንድ አመራር አባላት የተሰማኝን ለመግለጽ አስቤ ፤ያሰብኩትን በማድረጌ ይህ እውነት በዚህ ለመላው ህዝባችን አማራጭ የመረጃ ምንጭ በሆነ ሬዲዮ ይተላለፍ ይሆን? ወይንስ ይስተጉዋጎል ይሆን? የሚለው ነበር ፍርሃቴ
ምክንያቱም ይህ ነገር መራገብ በያዘበት ሰሞን ለማንም አለማድላቱን ልብ ይሉዋልና ነው የእኔን የግለሰቡን ነጻ አስተያየት ያፍንብኝ ይሆን ወይ? የሚለው የሚያሰጋኝ አንሶ ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ በዚያ ሰሞን ይህ የህዝብ ልሳን አይንና ጆሮ የሆነው ሚስጥር አያመልጤ የሆነው ሬዲዮ ሰማይና ምድርን እማኝ አድርጎ ለማንም በምንም ሁኔታ የሚያደላ አለመሆኑን ማረጋገጡን ሰማሁና ምን አልባት ይህ ነጻ የሆነው ከማንም በምንም ሁኔታ ያልተጣባ አስተያየቴ ወገንተኛነት ይንጸባረቅበታል ብለው የቅርጫት እራት ቢያደርጉትስ? የሚለው ሃሳብ እየተደጋገመ እየመጣብኝ ፍርሃቴን ጨመረው
በመቀጠል ለዚህ ሃሳቤ መንደርደሪያ እንዲሆነኝ ሳነብ ያገኘሁትን የፖለቲካ ፓርቲዎች አጀማመርና ውህደት ላይ ያላቸው ፍርሃት መተባበራቸውን እየነሳ አንጃዎችን ሲያበቅሉ ከተስተዋሉበት የትናንት ታሪካችን ጠቀስ አድርጌ ለማዋዛት እሞክርና ወደ ዋናው ቁም ነገር አልፋለሁ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ በሥልጣን ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሊያከብሩለት፣ ሊጠብቁለት ከሚገቡት መብቶቹ አንዱ በሕግና በደንብ ተደራጅቶ፣ ፓርቲ አቃቁሞ በሐገሩ የመንግስት አስተዳደር እንዲሳተፍ ማድረግ ነበር፡፡ ይህን አለማድረጋቸው መንግስታቸውን ለረዥም ጊዜ ለተካሄደ መፈንቅለ መንግስት እንዲጋለጥ፣ ለእሳቸውና ብዙ የንጉሱ ባለሥልጣናት መረበሽ፣ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ላለው የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ መመሰቃቀል ምክንያት ሆኗል ብለው የሚያስቡና የሚናገሩ ሰዎች መኖራቸውን በተለያየ አጋጣሚ ስንሰማ ነበር እውነትም በንጉሱ አገዛዝ ዘመን የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማቋቋም ተችሎ ቢሆን ኑሮ፣ ሕዝቡ ስለ ፓርቲ አሰራርና አመራር የተሻለ ልምድ ይገነባ እንደነበር ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አመሰራረትና አሰራር ባልታወቀባት ባልተለመደባት ኢትዮጵያ፣ በ1966 ዓም የካቲት ወር የፈነዳው ሕዝባዊ አመፅ የሚመራወ የተደራጀ ክፍል ባለመኖሩ የተጓዘው በስሜትና ፍላጐት እንደነበር እና አጋጣሚውን ተጠቅሞ ከአስተባባሪነት ወደ መንግስትነት ከፍ ከፍ እያለ የመጣው ደርግ መንግስት የሆነው እሱም ደጋግሞ እንደተናገረው ቤቱ ወይም መስመሩ ባዶ ስለነበር ነው፡፡ የነፃነት ግንባሮች ሆኑ በሐገራችን የፖለቲካ ፓርቲ ታሪክ ውስጥ በቀደምትነት የሚጠቀሱት ኢህአፓ መኢሶን፣ ኢጭአት፣ ኢኮፓ ወዘተ ሁሉም የፖለቲካ ልምዳቸው ከተማሪ ቤት ህይወታቸው የጀመረ ስለመሆኑ የሚተርኩልንም የዚያን ዘመን ትውልዶች አሉ የዚያን ግዜ የፓርቲዎቹ ምስረታ በሕግ በተፈቀደ መንገድ ባለመሆኑ በህቡና በአመፅ በመሆኑ አንድ አይነት አስተሳሰብ አንድ አይነት የትግል መሥመር ላይ ቁመው በመካከላቸው መተባበርና መዋሐድ ሳይፈጥሩ ሁሉም እኔ ነኝ ትክክል እንዳሉ፣ ያንን ለውጥ ዘመን ያሳለፉ ፓርቲዎች መሆናቸው ዛሬ ላለንበትና ለደረስንበት የፓርቲዎች እንተባበር እንቀናጅ የማለት የመተባበር መንፈስ አስተምህሮት ሰጥቶ አልፎዋል ፓርቲዎቹ በግልፅ በአደባባይ በሕጋዊ መንገድ የተቋቋሙ ባለመሆናቸው እያንዳንዱ አባል የሌላውን ፓርቲ አባል ማወቅ የሚችልበት መንገድ እምብዛም ባለመኖሩ፣ አንድ ሰው የሁለት ፓርቲዎች አባል የሚሆንበት ሁኔታ ይፈጠር ነበር ይህ አይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የአንደኛው ፓርቲ አባል በሌላኛው ፓርቲ ውስጥ ችግር አስከትሏል፡፡ ይህ ብዙ ፓርቲዎች ውስጥ ከፍተኛ ጥፋት እንዲከተል ከማድረጉ በላይ፣ ፓርቲዎች እርስ በእርስ እንዳይተማመኑ የሚያደርግ መጥፎ ልማድ ተክሎ አልፏል፡፡ ኢህአዴግ በ1983 ዓም ከጫካ አዲስ አበባ ገብቶ የመንግስት ሥልጣን ከያዘ በኋላ ያፀደቀው ቻርተር የመደራጀት መብት ስለሚፈቅድ በሐገር ውስጥ በርካታ የፖለቲካ ድርጅቶች እንዲመሰረቱ መንገድ ከፍቷል፡፡ እጅግ ብዙ የብሔረሰቦች ጥቂት የብሔር ድርጅቶችም ለመመሥረት ችለዋል፡፡ እንደ ወላይታ፣ ከምባታ፣ ሐድያ፣ ሲዳሞ፣ አፋር ቤንሻንጉል ወዘተ ባሉ ብሔረሰቦች ስም የሚንቀሳቀሱ ሁለት ፓርቲዎች እየተፈጠሩ በመምጣታቸው የፖለቲካ ትግሉን ይብስ አደጋ ላይ መጣል ጀመሩ፡፡ ሕዝብ ላይ ተቃውሞ በመሰማቱ የመተባበር ጥያቄ እየጐላ መጣ፡፡ የደቡብ ሕብረትና የአማራጭ ኃይሎች ምስረታ ከተቃዋሚዎች በኩል የሚጠቀስ ሲሆን፣ በኢህአዴግ በኩል ደግሞ የኢህአዴግ መመሥረት የሚታወስ ነው፡፡ ምን አልባትም ወያኔ ሥልጣኑም ጉልበቱም ስላለው ሊሆን ይችላል፡፡ በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል፣ በአፋር ወዘተ የነበሩ የተቃዋሚ የብሔር የፖለቲካ ድርጅቶች ብዙዎች ከኢህአዴግ ተዋህደው አጋር ድርጅት ሆነዋል በተለይ ከ1993 ዓም ወዲህ የተለየ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውህደቶች የሚያረካ ውጤት ማሳየት ባለመቻላቸው «ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ» የሚል ሕዝባዊ ተቃውሞ ከዳር ዳር ተቀሰቀሰ፡፡ በ1997 ዓም ምርጫ ላይ ከስልሳ ያላነሱ የብሔርና የሕብረ ብሔር ድርጅቶች ለውድድር ቢቀርቡም፣ ሕዝብ ድምፅ የሰጣቸው ለአራት ድርጅቶች ብቻ ነው፡፡ እነሱም ቅንጅት፣ ኢህአዴግ፣ ሕብረትና |