|
ቅንጅትን የመቀልበስ ሴራ ከወያነ ጋር እየተካሄደ ነው |
|
|
|
Tuesday, 01 January 2008 |
|
አዲስ አበባ ፡- በቅርቡ በቅንጅት ሊቀመንበር በኢ/ር ኃይሉ ሻውል ከስራ የታገዱት የአመራር አባላት ከገዢው ፓርቲ ተወካዮች ጋር በሚስጢር ድርድር መጀመራቸው ተሰማ። ከአዲስ አበባ ባገኘነው መረጃ መሰረት ድርድሩን መሪዎቹ ያደረጉት ውክልናውን ማን እንደሰጣቸው ባይታወቅም በቅንጅት ስም እንደሆነ ታውቁአል። በዚህ ድርድር በቅንጅት ስም የቀረቡት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳና ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ሲሆኑ ከወያነ በኩል ደግሞ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃነ ኃይሉ ናቸው ተብሉአል። በባ ፡- በቅርቡ በቅንጅት ሊቀመንበር በኢ/ር ኃይሉ ሻውል ከስራ የታገዱት የአመራር አባላት ከገዢው ፓርቲ ተወካዮች ጋር በሚስጢር ድርድር መጀመራቸው ተሰማ።
በዚህ ስብሰባ ከገዢው ፓርቲ በኩል ይገኛሉ ተብሎ የነበረው በረከት ስምኦን ለጊዜው ይፋ ባልሆነ ምክንያት አልተገኙም።
ሁለቱ ወገኖች በእስካሁኑ ንግግራቸው መረጃውን ይፋ ባለማድረግና በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን የዜናው ምንጭ ገልጹአል። በዚህም መሰረት "አክራሪ" ሲሉ የአገዛዙ ባለስልጣናት የሚወነጅሉአቸውን የቅንጅቱን የአመራር አባላት ከፓርቲው በማስወገድ ረገድ በጋራ ለመስራትም ተስማምተዋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በፓርቲው ጽ/ቤትነት የሚያገለግለውን ቢሮ በየትኛውም መንገድ ለመንጠቅ የሚደረገውን ጥረት ማሳካት የሚቻልበትን ሁኔታ ለማካሄድ ስለሚወሰዱ ርምጃዎችም ተነጋግረው ከስምምነት መድረሳቸው ተያይዞ ተገልጹአል። በተጨማሪም እነ ብርቱካን ሚደቅሳ እና ኢ/ር ግዛቸው በበኩላቸው በዚህ መሰል ሁኔታ ንግግር ማድርጋቸው በህዝቡ ዘንድ ተቃውሞ ሊያስነሳ ይችላል በሚል ቀደም ሲል ቅንጅቱ ያቀረባቸውን ስምንት ጥያቄዎች በማንሳት በነዚህ ላይ መነጋገር እንደሚፈልጉ ተደርጎ እንዲገለጽላቸው መጠየቃቸውንም ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ተችሉአል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ እነዚህ ግለሰቦች ጥቂት ሰዎችን በማስተባበር ጽ/ቤቱን በሃይል ለመቆጣጠር ተደጋጋሚ ጥረቶችን አድርገው ሳይሳካላቸው መቅረቱን መዘገባችን ይታወሳል።በዚህ ዙሪያ የሚካሄደውን ድብቅ ሴራ እና ብዙ ህዝብ የሞተለትን ትግል በመቀልበስ ያገዛዙ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚካሄደውን ደባ ወደፊት እየተከታተልን ለማቅረብ የምናደርገውን ጥረት እንቀጥላለን።
|