RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow ብርቱካንና የፓርላማ አባላቱ ሳይስማሙ ቀሩ
ብርቱካንና የፓርላማ አባላቱ ሳይስማሙ ቀሩ Print E-mail
Monday, 11 February 2008

 

ከጌታቸው ንጋቱ

የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ የፓርላማ ተመራጭ የሆኑ አባላት ከወ/ሪት ብርቱካን ጋር ያደረጉት ንግግር ያለስምምነት ተቋጨ፡፡ እነ ወ/ሪት ብርቱካን የላዕላይ ምክር ቤት መምረጥ አይችሉም፤ የጠቅላላ ጉባኤው ስልጣን ነው ሲሉ የፓርላማ አባላቱ ተናግረዋል፡፡

 

የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ የፓርላማ ተመራጭ የሆኑ አባላት ከወ/ሪት ብርቱካን ጋር ያደረጉት ንግግር ያለስምምነት ተቋጨ፡፡ እነ ወ/ሪት ብርቱካን የላዕላይ ምክር ቤት መምረጥ አይችሉም፤ የጠቅላላ ጉባኤው ስልጣን ነው ሲሉ የፓርላማ አባላቱ ተናግረዋል፡፡

ሰኞ ዕለት ቄራ አካባቢ በሚገኘውና እነ ወ/ሪት ብርቱካን ለመሰብሰቢያና ለመገናኛነት በሚጠቀሙበት የኪራይ ቤት ውስጥ የሃያ አምስት ፓርላማ አባላት ውክልና አለን የሚሉ አምስት የፓርላማ አባላት ከወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳና ከአቶ አለማየሁ የኔነህ ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል፡፡

የፓርላማ አባላቱን ወክለው ለኤ.ቢ.ቢአይ ዊክሊ መግለጫ የሰጡት አቶ ጌታቸው ባይፈርስ እንደገለፁት “ወደእነ ወ/ሪት ብርቱካን የሄድነው እያደረጉ ያለውን እንቅስቃሴ ተገቢ ባለመሆኑ እንዲያቆሙ፤ የላዕላይ ም/ቤት መምረጥ የሚችለው ጠቅላላ ጉባኤው እንጂ እነሱ አለመሆናቸውን ለማስረዳት ነበር፡፡ አዲስ ፓርቲ መመስረትም ከጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ ውጪ በመሆኑ ከዚህ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ ጠይቀናል” ብለዋል፡፡

የፓርላማ አባላቱ ከዚህ በተጨማሪ ከአቶ ተመስገን ጋር የወ/ሪት ብርቱካን ቡድን ያደረገውና እያደረገው ያለው ውህደት አግባብ አለመሆኑንና ሂደቱ ቅንጅትንና የኢትዮጵያን ሕዝብ የመታገል መንፈስ የሚገድል በመሆኑ መቆም እንዳለበት መጠየቃቸውን አቶ ጌታቸው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የተጀመረው የሽምግልና ሂደትንና የዴሞክራሲ ጥረቱን የነወ/ሪት ብርቱካን አካሄድ እንደሚጎዳ እንደገለፁላቸው የሚናገሩት እኝሁ የፓርላማ አባል ከነወ/ሪት ብርቱካን በተሰጣቸው ምላሽ ደስተኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሪት ብርቱካን በሰጧቸው ምላሽም [በያዝነው መንገድ እንቀጥላለን፤ ሥራ መስራት ስላለብንም የላዕላይ ም/ቤቱን ማሟላታችን ትክክለኛ እርምጃ ነው] ማለታቸውን አቶ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡

ወ/ሪት ብርቱካንን ስለተደረገው ስብሰባ ለማነጋገር በትላንትናው ዕለት ያደረግነው ጥረት ስልካቸውን ባለመመለሳቸው ሊሳካ አልቻለም፡፡

http://www.abbimedia.com.et






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving