|
የኘሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የጎሣ ፖርቲ ያጣጥራል፡፡ |
|
|
|
Wednesday, 19 March 2008 |
|
ከታዲዎስ ታንቱ፣
በዓላማ ሳይሆን በዘር ተደራጅቶ ለአሥራ ስድስት ዓመታት በኘሮፈሰር በየነ ጴጥሮስ መሪነት ሲንቀሳቀስ የቆየው 14 ጎሳዎች በአባልነት የሚገኙበት የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ሕብረት በሚል ስያሜ የሚጠራው የጎሳ ፖርቲ በአሁኑ ወቅት ሊሞት እንደሚያጣጥር ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
እንደ ውስጥ አዋቂ ምንጮች አገላለፅ ፖርቲው አሥራ ስድስት ዓመታት ፈጽሞ ጠቅላላ ጉባዔ ያላካሔደ ከመሆኑም በላይ ኘሮፈሰሩ ከፖርቲው ይልቅ ራሳቸውን አገዝፈው ለማሳየት የሚያደርጉት ጥረት ፖርቲውን ለዚህ ውድቀት እንደዳረገው ተመልክቷል፡፡
በተዛመደ መልኩ ኘሮፈሰሩ የአመራር ችሎታ የሌላቸው ሲሆን፣ለፖርቲያቸው ትኩረት ከመስጠት ይልቅ ለራሳቸው ጎሳ ኑሮ መሻሻል አበክረው ሰለሚጨነቁ ፖርቲው እንደተጎዳ የሚናገሩ ጥቂት አይደሉም፡፡
በዚህ ምክንያት በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የሕብረቱ አባል ጎሳዎች ሕብረቱን ለቅቀው የወጡ ሲሆን ሌሎችም ለመውጣት እየተዘጋጁ መሆናቸውን የመረጃ ምንጮቻችን አክለው አስረድተዋል፡፡
ኘሮፈሰር በየነ በወያኔ ፖርላማ ጥልቀት በሌላቸው ሐሳቦች የቃላት ጂምናስቲክ በመሥራት የሚታወቁ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ ለሥርዐተ አገዛዙ ኘሬዝዳንትነት ተወዳድረው የወደቁ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
ግለሰቡ በ1988 ዓ/ም ተቋቁሞ አንዳች ቁም ነገር ያልሰራውን አማራጭ ኃይሎች የተባለውን ስብስብ ሲመሩ የቆዩ ሲሆን፣ ሰብስቡ በአሁኑ ወቅት ሕልውናው በራሱ ጊዜ በመክሰሙ የምስክር ወረቀቱን ወስደው ለምርጫ ቦርድ መመለሳቸውንም ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሰውየው በወያኔ ሹማምንት ተገምግመው በቅርቡ ኘሮፈሰርነት ከማግኘታቸው በፊት በወያኔ የረዳት ኘሮፈሰርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸው በጎሳ አገዛዝ መርህ በተቀረፀው የትምህርት ፖሊሲ ሥርዓተ-አገዛዙን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለማስገንጠልና ኢትዮጵያን የባሕር በር ለማሳጣት በ1983 ዓ/ም በወያኔ የተረቀቀውን ቻርተር ተሽቀዳድመው የፈረሙት እኚህ ግለሰብ የሥርዓተ-አገዛዙ የትምህርት ማኒስቴር ምክትል ሚኒስቴር ሆነው አገዛዙን በታማኝነትና በቅንነት ለዓመታት ማገልገላቸውም ይታወሳል፡፡
|