RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow ኢንጅነር ኃይሉ የቅንጅት ኮሚቴ ሰብሳቢዎችን አነጋገሩ፣
ኢንጅነር ኃይሉ የቅንጅት ኮሚቴ ሰብሳቢዎችን አነጋገሩ፣ Print E-mail
Sunday, 13 April 2008
ከታዲዎስ ታንቱ      ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፖርቲ ኘሬዝዳንት የጎፋ ልዩ ዞን የቅንጅት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትንና የዞኑን የሰባት ወረዳ የፖርቲው ኮሚቴ ሰብሳቢዎችን ከዋሸንግተን ዲሲ መጋቢት 28 ቀን 2ዐዐዐ ዓ/ም በስልክ አነጋገሩ፡፡    ኘሬዝዳንቱ በዚሁ ዕለት ከዞኑ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፖርቲ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ለቀረበላቸው ልዩ ልዩ ጥቄዎችም በማብራራት መልስ እንደሰጡ ከሥፍራው ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡

   

 በመቀጠልም ኘሬዝዳንቱ በዞኑ ውስጥ ለሚገኙ ለደምባ ጎፋ፤ለሣውላ ከንቲባ፣ ለአይዳ፣ ለበስኬቶ ፣ ለመሎ ኮዛ፣ለዑባ ጥንስስና ለዛላ ወረዳዎች የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፖርቲ ኮሚቴ ሰብሰሳቢዎች የፖርቲውን የወቅቱን እንቅስቃሴ እንዲሁም በቅርቡ የሚካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በማስመልከት ገለጻ ያደረጉላቸው ሲሆን ከገለጻው በኋላ ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎችም በማብራራት ተገቢውን መልስ ሰጥተዋል፡፡    ኘሬዝዳንቱ ከጎፋ ልዩ ዞን የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፖርቲ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ጋር ሊወያዩ የቻሉት እነሱ ራሳቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መሠረት በማድረግ የፖርቲው ጽ/ቤት የግንኙነት ኘሮግራሙን በማመቻቸቱ መሆኑን የመረጃ ምንጮች አክለው ገልፀዋል፡፡    የጎፋ ልዩ ዞን የልዩ ልዩ ወረዳዎች የኮሚቴ ሰብሳቢዎች በኘሬዝዳንቱ ገለጻና ማብራሪያ ፖርቲው ሰለሚገኝበት ሁኔታ ተገቢውን ግንዛቤ በመጨበጣቸው በአሁኑ ወቅት ለማንኛውም ዓይነት ከፋፋይ እንደማይንበረከኩ ገልጸው በተረጋጋ ስሜት የጉባዔውን ቀን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውንም ለቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ጽ/ቤት በስልክ አረጋግጠዋል፡፡  




Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving