|
ተማሪው በወያኔ ታጣቂዎች ተገደለ - ታዲዎስ ታንቱ |
|
|
|
Friday, 16 May 2008 |
|
በደቡብ ጎንደር በፋርጣ ወረዳ በቁሃላ ገበሬ ማህበር ውስጥ ምሥጋናው ጌጤ ዘለለው የተባለ አሥራ ዘጠኝ ዓመት ዕድሜ የነበረው የስምንተኛ ክፍል ተማሪ በወያኔ ቅጥረኛ ፖሊሶችና በአካባቢው ታጣቂዎች በከፍተኛ ደረጃ ድብደባ ተፈጽሞበት ሚያዝያ 13 ቀን 2ዐዐዐ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን በሥፍራው የነበሩ የዓይን ምስክሮች አረጋግጠዋል፡
የዓይን ምሥክሮች ወጣቱ ተደብድቦ የተገለደበት ምክንያት ሰሞኑን ወያኔ ባካሔደው የአካባቢና የማሟያ ለተባለው ማስመሰያ ምርጫ" የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳይወጡ እየተዘዋወረ ቅስቀሳ አድርጓል" በማለት መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡
የሟች ምሥጋናው ጌጤ ዘለለው አስክሬን ቤተሰቦቹ የትምህርት ቤት ጓደኞቹና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት በአቱዕ ባዕታ ቤተ ክርስቲያን ሚያዝያ 14 ቀን 2ዐዐዐ ዓ/ም መቀበሩንም ከሥፍራው ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ተማሪ ምሥጋናው ጌጤ ዘለለው በተገደለበት ዕለት በርካታ ወጣቶች በፖሊሶች የተደበደቡ ሲሆን ከመካከላቸው ፀጋዬ ቢሆነኝና ማሩዬ መልኬ የተባሉ ሁለት ወጣቶች እግራቸውን ተሰብረው ከቦታ ወደ ቦታ የሚንቀሳቀሱት ታዝለው መሆኑንም የመረጃ ምንጮቻችን አክለው አስረድተዋል፡፡
|