|
የድሬዳዋ ዞን የቅንጅት ጽ/ቤት በፖሊስ ኮሚሽን ላይ ክስ መሠረ |
|
|
|
Friday, 23 May 2008 |
|
የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የድሬዳዋ ዞን ጽ/ቤት በድሬዳዋ ጊዜአዊ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ላይ ሰሞኑን ክስ መመሥረቱን ከድሬዳዋ የደረሱን የመረጃ ምንጮች አመለከቱ፡፡
ጽ/ቤት በፖሊስ ኮሚሽን ላይ ክስ ሊመሠረት የቻለው በሕጋዊ መንገድ የዕለት ተዕለት ተግባሩን በማከናወን ላይ በነበረበት ወቅት ያለ አንዳች ምክንያት ፖሊሶች ጽ/ቤቱን በመዝጋት እንዲከፍቱት በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ፈቃደኝነት ባለማሳየታቸው መሆኑን የመረጃ ምንጮች አክለው አስረድተዋል፡፡
የዞኑ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክሲ ፓርቲ ጽ/ቤት ቀደም ሲል ጽ/ቤቱ መዘጋቱ አግባብ ያለ መሆኑን በመግለፅ በአስቸኳይ እንዲከፈት ለድሬዳዋ ጊዜአዊ አስተዳደር ለፍትሕ፣ ለፀጥታና ለሕግ ጉዳዮች ቢሮ አመልክቶ ተገቢ መልስ እንዳልተሠጠው ከመረጃ ምንጮች ለማወቅ ተችለል፡፡
ጽ/ቤቱ ባሁኑ ወቅት አምሥት የሠነድ ማስረጃዎችና አራት የሰው ምሥክሮች ለፍርድ ቤት ያቀረበ ሲሆን ተከሣሽ ለግንቦት 15 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም መልሱን ይዞ እንዲቀርብ መጥሪያ የተላኩለት መሆኑንም የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
|