RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Friday
Nov 21st
Home arrow News arrow ወዝ አደሮች ከጃዊ በግዴታ እንዲወጡ ተደረገ
ወዝ አደሮች ከጃዊ በግዴታ እንዲወጡ ተደረገ Print E-mail
Friday, 23 May 2008

      በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ውስጥ በጉልበት ሥራ የሚተዳደሩ የቤንሻንጉል ተወላጆች ለብዙ ዓመታት ከኖሩበት ከጃዊ ከተማ በግዴታ ወደ ትውልድ ሠፈራቸው ሰሞኑን እንዲመለሱ መደረጉን የዓይን ምሥክሮች አመለከቱ፡፡

      የምዕራብ ጎጃም የአገዛዝ አካላት ለምን የጉልበት ሠራተኞች ከጃዊ እንዲወጡ እንደሚገደዱ ተጠይቀው ሲመልሱ "ሁሉም በትውልድ ቀዬው ይሥራ!" የሚል አጭር የዘረኝነት መልስ መስጠታቸውንም የዓይን ምሥክሮች አክለው አስረድተዋል፡፡

 

      አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የቤንሻንጉል ተወላጆች ከጃዊ እንዲወጡ ስለመደረጋቸው በሰጡት አስተየየት "የአማራን ሕዝብ ዘረኝነት ማስተማር በፍፁም ስለማይቻል ገዥዎች በከንቱ ይደክማሉ፡፡" በማለት መናገራቸውንም ከወደ ምዕራብ ጎጃም ከደረሱን መረጃዎች ለማወቅ ተችሏል፡፡

      በሌላም በኩል በቤሻንጉል ክልል በመተከል ዞን በፓዌ ወረዳ በጣና በለስ ጣሊያን በሠራቸው ቤቶች ውስጥ ለብዙ ዓመታት የኖሩ ዜጎችን የወያኔ ሹማምንት ለቅቀው እንዲወጡ ማስገደዳቸውን ሰሞኑን ከውጭ ፓዌ የደረሱን መረጃዎች አመለከቱ፡፡

      ባሁኑ ወቅት በዚሁ አስገዳጅ ትዕዛዝ መኖሪያቸውን ለቅቀው የወጡ አያሌ ዜጎች መጠለያ አጥተው ሜዳ ላይ የፈሰሱ ሲሆን የአገዛዙ ሹማምንት ለተፈናቃዮቹ ምንም የሠጧቸው ተስፋም እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል፡፡

      ይህ በእንዲህ እንዳለ ዕህል ከአማራ ክልል ወደ ቤንሻንጉል እንዳይገባ የአገዛዝ አካላት በመከልከል ላይ እንደሚገኙ የዓይን ምሥክሮች ከቦታው በስልክ አስታውቀዋል፡፡

      በዚህ ምክንያት ባሁኑ ወቅት በቤንሻንጉል ክልል በመተከል ዞን በፓዌ ወረዳ በከፍተኛ ደረጃ የዕህል እጥረት እንደሚታይ ለማወቅ ተችሏል፡፡

     






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving