RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Thursday
Aug 21st
Home arrow News arrow ሕዝቡ ከሱዳን ጦር ጋር እየተዋጋ መሆኑ ተገለጠ
ሕዝቡ ከሱዳን ጦር ጋር እየተዋጋ መሆኑ ተገለጠ Print E-mail
Monday, 07 July 2008

     በሰሜን ጎንደር ዞን በቋራና በሑመራ ወረዳዎች ውስጥ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ ከገባው ከሱዳን ጦር ጋር ሕዝቡ በመዋጋት ላይ እንደሚገኝ ሰሞኑን ጦርነቱን ሸሽተው የመጡ የዓይን ምስክሮች ገለጡ፡፡

     የወያኔን ሥርዓተ አገዛዝ መከታ አድርጎ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ የገባው ይህ የሱዳን ጦር በሕዝቡ ንብረት ላይ ከፍተኛ ዘረፋ ያካሄደ ሲሆን ከወገን በኩል የሞቱና የቆሰሉ መኖራቸውንም የዓይን ምሥክሮች አረጋግጠዋል፡፡

 

     እንደ ዓይን ምሥክሮች አገላለፅ ጦርነቱ ከዛሬ 12 ቀን በፊት ተቀስቅሶ አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን በወረዳዎቹ ውስጥ የሚገኙ የኢትዮጵያ የሥርዓተ- አገዛዙ ጦር አባላት ግን ከማንም ሳይወግኑ በገለልተኝነት መቆማቸው ተመልክቷል፡፡

     ባአሁኑ ወቅት የሁለቱን ሀገሮች ድንበር እንደገና ማካለል በሚል ሰበብ የወያኔ አገዛዝ መሬት ከኢትዮጵያ ቆርሶ ለሱዳን ሊሰጥ ማቀዱን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ሁኔታ በመቃወም ላይ ሲገኝ በውስን ደረጃ የሥርዓተ- አገዛዙ ታጣቂዎችም በግልፅ ተቃውሞ እያቀረቡ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

     ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ደጋማው ክፍል ካድሬዎች እንዲሁም የሥርዓተ - አገዛዙ አካላት ስለሱዳንና ኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያትተውን ሰነድ አዘጋጅተው ከላይ የተጻፈውን ዝርዝር ደብቀው በመያዝ አርሶ አደሮችን እያስገደዱ በማስፈረም ላይ መሆናቸውን የዐይን ምሥክሮች ከቦታው ገለጡ፡፡

     አንዳንድ ውስጥ ዐዋቂዎች ይህ ሰነድ አርሶ አደሮች መሬቱ ለሱዳን ተቆርሶ እንዲሰጥ የተስማሙ ለማስመሰል የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Other top stories


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving