|
Monday, 07 July 2008 |
|
ወያኔ የሥልጣን ዕድሜውን ለማቆት ለዓመታት ዐቢይ የፕሮጋንዳ መነሻ አድርጎ ይጠቀምበት የነበረው የግምባታ ሥራ ከሰኔ ወር 2000 ዓ.ም አንስቶ ተቋረጠ፡፡
የግንባታ ሥራ እንቅስቃሴ የተቋረጠው የስሚንቶ ዋጋ ከመጠን በላይ በመናሩ ምክንያት መሆኑ የታወቀ ሲሆን ወያኔ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡
ባሁኑ ወቀት አንድ መቶ ኪሎግራም ስሚንቶ ከብር 380 እስከ 400.00 የሚሸጥ ሲሆን በዚህም ዋጋ በተፈለገው መጠን ማግኘት እንደማይቻል ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወያኔ ላለፉተ አሥራ ሰባት ዓመታት በአዲስ አበባና በክፍላተ -ሀገር የኢትዮጵያን ሕዝብ መሬት ለዘሮቹና ለአሽከሮቹ በማከፋፈል ፎቆችን ሲያሰራ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በሌላም በኩል የጋዜጠኝነት ሙያን ሥነ ምግባር ጨርሶ በመተው በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ክፉኛ ለተጠላው ለወያኔ አገዛዝ በመሣሪያት ከመዝለቅ ያለፈ አንዳችም ዓላማ የሌላቸው ጋዜጠኛ ተብዬ የሥርዓተ - አገዛዙ ፕሮፓጋንዲስቶች ባሁኑ ወቀት ስለ ምግብ ዕህል በመገናኛ ብዙሃን መዘገብ ትተዋል፡፡
ፕሮፓጋንዲስቶቹ ስለዚህ ጉዳይ መዘገቡን ሊተው የቻለው በየዕለቱ እያሻቀበ ስለሚሄደው ስለምግብ ዕህል ዋጋ ለመዋሸት ፈጽሞ የማይመች በመሆኑ እንዲህ ዓይነት ዘገባ ከመዘገብ እንዲቆጠቡ ከጌቶቻቸው በደረሳቸው ትዕዛዝ ምክንያት መሆኑን የውስጥ ዐዋቂ ምንጮች ተናግረዋል፡፡
የችጋር መልዕክተኛ የሆነው ወያኔ በ1983 ዓ.ም እየግተለተለ አዲስ አበባ ሲገባ በብር 180.00 ይሸጥ የነበረው አንድ መቶ ኪሎ ግራም ነጭ ጤፍ ባኑ ወቀት በብር 1200.00 የሚሸጥ ሲሆን ዛሬ እስከ ብር 400.00 ድረስ የሚያወጣው አንድ መቶ ኪሎ ግራም ሲሚንቶ ደግሞ በዚያን ጊዜ በብር 38.00 ይሸጥ እንደነበር ይታወሳል፡፡
|