|
ሶስት የቅንጅት አባላት በሰርቪያ ውስጥ መታሰራቸው ተገለጠ |
|
|
|
Thursday, 17 July 2008 |
|
ለአትሌቲክስ ውድድር ተመልምለው ውጭ ሀገር ሲደርሱ ከጨካኙ የወያኔ መንግስት አፈንግጠው የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቁት ሶስት የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባላት በሰርቪያ ቤልግሬድ ውስጥ ከጥር ወር 2000 ዓ.ም አንሥቶ በእስር ላይ እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ሰሞኑን ገለጡ፡፡
እንደ ቤተሰቦቻቸው አባባል አትሌቶቹ ተይዘው ሊታሰሩ የበቁት "በኢትዮጵያ ምንም የፖለቲካ ችግር የለም!" በሚሉ ፖሊሶች ሲሆን ይዘው ለፖሊሶች የሰጧቸው ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሠራተኞች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት በዚህ ሁኔታ በእስር ላይ የሚገኙት፡- 1.ታአምራት ተስፋዬ 2. ብርሃኑ ዮሀንስ 3.አንዲት ስሟ ለጊዜው የማይታወቅ ሴት ሲሆን ተገቢውን ሕክምና መከልከላቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአትሌቶቹ ቤተሰቦች በአሁኑ ወቅት በአትሌቶች ላይ የከፋ ችግር ሊደርስባቸው እንደሚችል በጣም የሰጉ መሆናቸውን ገልፀው ዓለም አቀፍ ስብዓዊ መብት ተከራካሪዎች፣ ሰላም ወዳዶችና ዴሞክራቲክ ኃይሎች አትሌቶቹ በአስቸኳይ በነጻ እንዲለቀቁ አስፈላጊውን ግፊት ሁሉ እንዲያደርጉ በአጽንኦት ጠይቀዋል፡፡
|