RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow አባቷ የቅንጅት አባል በመሆናቸው እርዳታ ተከለከለች
አባቷ የቅንጅት አባል በመሆናቸው እርዳታ ተከለከለች Print E-mail
Thursday, 17 July 2008

     በደቡብ ኢትዮጵያ በጎፋ ልዩ ዞን በደምባ ጎፋ ወረዳ በያላ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ነዋሪ የሆነች ብርቱካን ብርሃኑ የተባለች አንዲት መናገርና መስማት የተሳናት ሴት አባቷ አቶ ብርሃኑ ኃይሌ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ ሰብዓዊ እርዳታ መከልከሏን የዓይን ምስክሮች ሰሞኑን ገለጡ፡፡

 

     እንደ የዓይን ምስክሮች አገላፅ ብርቱካን ብርሃኑ ማንነቱ በውል በማይታወቅ ሰው ተደፍራ የወለደችው የስምንት ወር ህፃን ያላት ሲሆን አባቷ ልጃቸው እርዳታ እንዲሰጣት አቶ ዘነበ ዘዋን የያላ ቀበሌ ሊቀመንበርን ደጋግመው ቢጠይቋቸውም ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

     በተያያዘ መልኩ ወይዘሮ ደስአለኝ ቱቶ የቀበሌው ሥራ አስኪያጅ ለዚህች ምስኪን ሴትና ለስምንት ወር ሕፃን ልጇ እርዳታ መከልከሉን በመደገፋቸው የአካባቢያቸው ነዋሪ ሴቶች በከፍተኛ ንቀትና ትዝብት እንዳዮዋቸው ከቦታው የደረሱን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

     ባሁኑ ወቅት እናትና ልጅ በከፍተኛ ችግር ላይ የሚገኙ መሆናቸውን አስረድተው በሰብዓዊነት አቋም ማንም ሰው እርዳታ ሊያደርጉላቸው እንደሚገባ የዓይን ምስክሮች አክለው ተናግረዋል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving