RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow በሰሜን ጎንደር ሕዝቡ በረኃብ መጠቃቱ ተገለጠ
በሰሜን ጎንደር ሕዝቡ በረኃብ መጠቃቱ ተገለጠ Print E-mail
Thursday, 17 July 2008

     በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት በወገራና በጎንደር ዙሪያ ወረዳዎች ውስጥ ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ በረኃብ መጠቃቱን የውስጥ ዐዋቂ ምንጮች ሰሞኑን ከሥፍራው አመለከቱ፡፡

 

     እንደ የውስጥ ዐዋቂ ምንጮች አገላለፅ በወገራ ወረዳ ቤተሰቦቻቸው በረኃብ ሲያልቁ ላለማየት የቆረጡ አባወራዎች ለአያሌ ዓመታት የኖሩበትን ቀዬ ለቅቀው በመሰደድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በዳባት ወረዳ በጨርብሣ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ደግሞ የሥርዓተ አገዛዙ አካላት በምግብ ለሥራ መርሐ-ግብር ሁለት ወር ሙሉ አሰርተው በነፍስ ወከፍ 1ዐ ኪሎ ግራም ጤፍና 1 ሊትር ዘይት ብቻ በመስጠታቸው ሕዝቡ ቅሬታውን በመግለፅ ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

       እንዲሁም በጎንደር ዙሪያ ረኃብ በማየሉ ሕዝቡ በአብያተ ክርስቲያንና በመስጊዶች በመሰብሰብ ክርስቲያኑ ህብረተሰብ ብር 15.ዐዐዐ /አሥራ አምስት ሺህ/ ሙስሊሙ ደግሞ ብር 3ዐ.ዐዐዐ /ሰላሳ ሺህ/ አዋጥቶ በነዋሪዎች መካከል በኑሮ ደረጃቸው እጅግ ችግርተኛ ለሆኑ እርዳታ ለማድረግ የራሱን ኮሚቴ በማቋቋም በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ከጎንደር ከተማ ምንጮች አክለው ገልጠዋል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving