RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow በጌዴኦ ዞን አንድ የቅንጅት አባል ተገደለ
በጌዴኦ ዞን አንድ የቅንጅት አባል ተገደለ Print E-mail
Sunday, 20 July 2008

   

በደቡብ ኢትዮጵያ በጌዴኦ ዞን በወናጎ ወረዳ በዓለም ሆቴል ቤት ውስጥ በአስተናጋጅነት ተቀጥሮ ይሠራ የነበረ አስቻለው ባዬ የተባለ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል በአንድ የወያኔ ፖሊስ አባል በተተኮሰ ጥይት ሐምሌ 2 ቀን 2000 ዓ.ም ተገደለ፡፡

 

22 ዓመት ዕድሜ የነበረው ይህ ወጣት መገደሉን በመቃወም በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉንም የዐይን ምስክሮች ከስፍራው ገልፀዋል፡፡

በዚሁ ሕዝቡ ከወናጎ ተነስቶ እስከ ዲላ ድረስ ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ "ቅንጅትን መምረጥ ወንጀል አይደለም! እኛ ራሳችንን እናስተዳድራለን! ውጡልን!" የሚሉትና ተዛማጅ መፈክሮች የተያዙ ሲሆን ሰልፈኞቹ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ድረስ ዘልቀው ተቃውሞአቸውን ማሰማታቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

የወጣት ሀብታሙ ባዬ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በወናጎ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቁጥሩ የበዛ ሕዝብ በተገኘበት ሐምሌ 3 ቀን 2000 ዓ.ም ተፈፅሟል፡፡

     በተመሳሳይ ዜናም በደቡብ ኢትዮጵያ በጌዴኦ ዞን በወናጎ ወረዳ በወናጎ ከተማ ከአንድ ወር በፊት መሐመድ በተባለው የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፖርቲ ደጋፊ ላይ ሽጉጥ ተኩሶ አንድ እግሩን በጥይት የሰበረው ባሻ ተረፈ ኡዴ የተባለ የሥርዓተ-አገዛዙ አገልጋይ በሕዝቡ አስገዳጅነት ሐምሌ 3 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም ተይዞ መታሰሩን ከወናጎ የደረሱን የመረጃ ምንጮች አመለከቱ፡፡

     ባሻ ተረፈን አስገድዶ በመያዝ እንዲታሰር ለፖሊስ ያስረከበው በወናጎ ከተማ ውስጥ አስቻለው ባዬ የተባለው የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል ሐምሌ 2 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም በአንድ የፖሊስ ባልደረባ መገደሉን በመቃወም ለሰላማዊ ሰልፍ የወጣው ሕዝብ መሆኑን ምንጮች ከወናጎ ገልፀዋል፡፡

     ታሣሪው ባሻ ተረፈ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከእሥር ቤት እንዳይለቀቅ ህብረተሰቡ ራሱ ክትትል በማድረግ ላይ መሆኑንም ምንጮች አክለው አስረድተዋል፡፡

     እግሩን በጥይት የተሰበረው ወጣት መሐመድ የአንድ ልጅ አባት ሲሆን ባሁኑ ወቅት የአልጋ ቁራኛ ሆኖ መቅረቱንም የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving