RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow አንድ የቅንጅት ደጋፊን የገደለው እጁን ሰጠ
አንድ የቅንጅት ደጋፊን የገደለው እጁን ሰጠ Print E-mail
Thursday, 24 July 2008

     በደቡብ ኢትዮጵያ በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ በዋላሜ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ቱሬ ዲኦ የተባሉትን የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ደጋፊን ሐምሌ 5 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም በጥይት ገድሎ የተሰወረው ለማ የተባለ የሥርዓተ አገዛዙ የቀበሌ ታጣቂ ከሕግ ሊያመልጥ እንደማይችል አውቆ ሰሞኑን በሲዳማ ዞን ለጭኮ ወረዳ ፖሊስ እጁን ሰጠ፡፡

 

     በሥልጣን ላይ ላለው አገዛዝ የማምለክን ያህል ፍቅር የነበረው ይህ ነፍሰ ገዳይ ወንጀሉን ፈፅሞ እስከ ተሰወረበት ዕለት ድረስ በዲላ ዙሪያ ወረዳ በዋላሜ ቀበሌ ማህበር ውስጥ የጦር መሣሪያ ታጥቆ ንፁሐን ዜጎችን ሲያፈራራ የኖረ መሆኑ ታውቋል፡፡

     ግለሰቡ ቱሬ ዲኦን በጦር መሣሪያ መግደሉ እንደተሰማ የዲላና የአካባቢው ሕዝብ በቁጣ ገንፍሎ ወደ መኖሪያ ቤቱ በማምራት ቤቱን አፈራርሶ እንዳልነበረ ማድረጉንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

     የቱሬ ዲኦ የቀብር ሥነ ሥርዓት በጌዴኦ ዞን በአባያ ወረዳ በሜኤሣ ቀበሌ ውስጥ ሐምሌ 6 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም መፈፀሙ ታውቋል፡፡

     አንዳንድ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በጌዴኦ ዞን ውስጥ ንፁሐን ዜጎች በየወቅቱ በአገዛዙ ቅጥረኛ አገልጋዮች መገደላቸው  ክፉኛ ያስቆጣቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

     ቀደም ሲል በዚሁ ዞን በወናጎ ወረዳ በወናጎ ከተማ አስቻለው ባዬ የተባለ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል ባንድ ቅጥረኛ ፖሊስ ሲገደል እንዲሁም መሐመድ የተባለ የቅንጅት ፓርቲ ደጋሬ በዚሁ በወናጎ ከተማ ባሻ ተረፈ ኡዴ በተባለ ፖሊስ በተተኰሰ ጥይት እግሩን መሰበሩ ይታወሳል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving