|
በደቡብ ጎንደር አንድ የቅንጅት አባል ተገደለ |
|
|
|
Thursday, 24 July 2008 |
|
በደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወረዳ ወረታ ከተማ ውስጥ መልካሙ ክንድ አለም የተባለ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል ሐምሌ 1ዐ ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም ተገደለ፡፡
ይህን 21 ዓመት ዕድሜ የነበረውን ወጣት ሕይወት ያጠፉ ነፍሰ ገዳዮች እየተዝናኑ ሲሄዱ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ቢጠቁሙም ፖሊሶች ግለሰቦቹን ለመያዝ ፈቃደኛ ሳይሆኑ እንደ ቀሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወጣት መልካሙ በምርጫ 97 በወረታ ከተማ በታዛቢነት ተመድቦ የገዥው ፓርቲ አገልጋዮች ምርጫውን እንዳያጭበረብሩ ከፍተኛ ትግል ማድረጉ ታውቋል፡፡
የወጣት መልካሙ የቀብር ሥነሥርዓት በደቡብ ጎንደር በፋርጣ ወረዳ በምንዳጎ ተክለሐይማኖት ቤተክርስቲያን ሐምሌ 11 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም ተፈፅሟል፡፡
|