RSS 2.0 Email us: webmaster@mahder.com

Ethiopia: Mahder.com -Ultimate Ethiopian News and Information Portal

Saturday
Nov 22nd
Home arrow News arrow የቅንጅት አባላት በፍርድ ቤት ቀጠሮ መጉላላታቸውን ገለጡ
የቅንጅት አባላት በፍርድ ቤት ቀጠሮ መጉላላታቸውን ገለጡ Print E-mail
Friday, 25 July 2008

     ለሶስተኛ ጊዜ በተካሄደው በሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የአሸናፊውን የፖለቲካ ፓርቲ የምርጫ ውጤት በመቃወም በምርጫው አሸንፎ በሥልጣን ላይ ያለውን የወያኔ መንግሥት በዐመፅና በኃይል ከሥልጣን ለማውረድ እንዲሁም የሕገ መነግሥታዊ ሥርዓትን ተግባራዊነት ለማሰናከል አስበው የተንቀሳቀሱ መሆናቸውን በመግለፅ አቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተባቸው በሰሜን ወሎ ዞን በወልዲያ ከተማ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባላት ያለ አንዳች ውሳኔ ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር ወደ ፍርድ ቤት በመመላለስ መጉላላታቸውን ሰሞኑን ለፓርቲው ጽሕፈት ቤት በላኩት ደብዳቤ ገለጡ፡፡

 

     አባላቱ ቀደም ሲል ሕገ መንግሥቱ ተጥሶ ሶስት ወር ሙሉ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታሰራቸውን ገልፀው ከዚያን ወዲህም ቢሆን የአቃቤ ሕግ ምስክር እንደሚቀርብባቸው እየተነገረ ለዘጠኝ ጊዜ ወደ ፍርድ ቤት መመላለሳቸውን አምርረው ተናግረዋል፡፡

     ተከሣሾቹ አቃቤ ሕግ በውስን ቀጠሮዎች ምስክሮቹን ማቅረብ ካልቻለ ፍርድ ቤቱ ፋይሉን ዘግቶ እነሱን በነፃ ሊያሰናብታቸው ይገባ እንደነበር ገልፀው ይህን ያህል ጊዜ ለአቃቤ ሕግ ዕድል መሰጠቱ ከፍተኛ መጉላላት እንዳደረሰባቸው አስረድተዋል፡፡

     በቀጠሮ ብዙ ተጉላልተው እስከ ዛሬ ባንድ ተከሳሽ ላይ አንድ የአቃቤ ሕግ ምስክር ብቻ መቅረቡን የገለፁት ተከሳሾቹ ወደ ፍርድ ቤት በመመላለስ የሥራ ጊዜአቸውን በከንቱ ከማባከናቸውም በላይ በወጪ ረገድ የደረሰባቸውም ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

     ተከሳሾቹ ባሁኑ ወቅት እነሱን አንገት በማስደፋት ፈርተው ከሕጋዊና ሰላማዊ ትግላቸው እንዲያፈገፍጉ የአገዛዙ ካድሬዎች እንዲሁም ደህንነቶች የሚፈፅሙትን ዛቻ፤ ማስፈራራትና ወከባ በመቋቋም ላይ መሆናቸውን አስረድተው በማያያዝም "እኛ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፖርቲ አባላት የትግላችን ዋንኛ አካል ህግና የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሀገር መፍጠር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡" ብለዋል፡፡

     ከፍተኛ መጉላላት የደረሰባቸው መሆኑን በመግለፅ ለቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ደብዳቤ ከጻፋት የፓርቲው አባላት መካከል ስምንቱ የመንግሥት ሰራተኞች፤ አምሥቱ በንግድ ሥራ የሚተዳደሩ፣ አምሥቱ ደግሞ አርሶ አደሮች ሲሆኑ የተቀሩት ተማሪዎች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡






Reddit!Del.icio.us!Facebook!Slashdot!Netscape!Technorati!StumbleUpon!Newsvine!Furl!Yahoo!Ma.gnolia!Free social bookmarking plugins and extensions for Joomla! websites! title=
Comments (0)Add Comment

Write comment
quote
bold
italicize
underline
strike
url
image
quote
quote
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley
Smiley

security code
Write the displayed characters


busy
 


Quick Jump

Ethio Date & Time

ዛሬ ቀኑ:

Calendar Converter




Daylight Saving