|
አንድ የቅንጅት አባል ፍትሕ ማጣታቸውን ገለጡ |
|
|
|
Sunday, 10 August 2008 |
|
አቶ እሸቱ ከበደ ሸንቁጥ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባል ንብረታቸውን በሥርዓተ-አገዛዙ ካድሬዎችና በግብረ አበሮቻቸው ተዘርፈው እስከ ዛሬ በሕግ አግባብ ተገቢውን ፍትሕ ያላገኙ መሆናቸውን ሰሞኑን ገለጡ፡፡
ቀደም ሲል በአርሲ ዞን በደዴታ ወረዳ በዴራ ከተማ በዐ1 ቀበሌ ነዋሪ የነበሩትና ባሁኑ ጊዜ ተባርረው በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙት አቶ እሸቱ ንብረታቸውን የተዘረፉት ሚያዝያ 4 ቀን 1998ዓ.ም ከሌሊቱ በ8 ሰዓት ላይ እንደነበር አስረድተው ከዚያን ጊዜ አንስቶ ለሥርዓተ-አገዛዙ የሕግ አካላት በተከታታይ ቢያመለክቱም ለጉዳያቸው ትኩረት የሚሰጥ አካል ማጣታቸውን በምሬት ተናግረዋል፡፡
በነበሩበት በዴራ ከተማ አራት ጊዜ ታሥረው የተፈቱ ከመሆናቸውም በላይ በቀን ሁለት ጊዜ ወደ ተዘጋጀላቸው ሥፍራ እየቀረቡ እንዲፈርሙ ይገደዱ እንደነበር የተናገሩት አቶ እሸቱ ቤተሰባቸውም ተበትኖ በከፍተኛ ችግር ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በጠቅላላው ከብር አሥር ሺህ በላይ ዋጋ የሚያወጣ ንብረት የተዘረፉ መሆናቸውን የገለፁት አቶ እሸቱ በመጨረሻም የሰብዓዊ መበቶች ድርጅቶችና የሚመለከታቸው አካላት በግፍ የተዘረፈው ንብረታቸው እንዲመለስላቸው የበኩላቸውን ግፊት ሁሉ እንዲያደርጉ አበክረው ጠይቀዋል፡፡
|