|
Monday, 06 October 2008 |
በመተከል ዞን በፓዌ ልዩ ወረዳ ውስጥ ንፁሐን ዜጎች በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት ብቻ የእርሻ መሬታቸውን መቀማታቸው ሰሞኑን ተሰማ፡፡
በዚህም መሠረት አድማሱ ቦራ በመንደር 5 የቀጣና 2፤ ጌታሁን አመኑ በመንደር 5 የአልሙ ከተማ፤ ታገለ እምቢያለ የመንደር 4፤ ሰይድ መሐመድ የመንደር 7፤ መሰለ ታደገ የመንደር 5 ነዋሪዎች የእርሻ መሬታቸውን ተቀምተው ባሁኑ ወቅት ከነቤተሰቦቻቸው በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በተመሣሣይ ሁኔታ ቢልልኝ አረጋ፤ ጌትነት መለሰ፤ ሰፈነ መኳንንት፤ ግርማ ታአምራት፤ ይልቃል ዓለሙ፤ ሀብታሙ ማሩ፤ ታአምሩ ይማም፤ መሐመድ ቢላል ሰይድ መሐመድ የተባሉ የመንደር 4 ነዋሪዎች መሬታቸውን ተቀምተው ባሁኑ ወቅት ለችግር መዳረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ሼህ መሐመድ ዘዋገ የመንደር 7፤ ጌታው ይታፈሩ በመንደር 7 የቀጣና 1፤ ካሣዬ ዘነበ በመንደር 7 የቀጣና 1፤ አጋጨው አምታታው በመንደር 17 የቀጣና 1፤ ደህንነት ሙጩ በመንደር 16 የቀጣና 1ና ጥሩዬ መሠለ በመንደር 24 የቀጣና 2 ነዋሪዎች የእርሻ መሬታቸውን በአገዛዙ አካላት ተቀምተዋል፡፡
|