|
መንግስት የመኢአድን የጎዳና ላይ ቅስቀሳ አገደ-ድብደባ ፈፀመ |
|
|
|
Sunday, 30 November 2008 |
|
መንግስት የመኢአድን የጎዳና ላይ ቅስቀሳ አገደ
በአባሎቹም ላይ እስራትና ድብደባ ፈፀመ፡፡
መኢአድ በአዲስ አበባ በምሥራቅና በምዕራብ ቀጣናዎች እያካሄደ ባለው የጎዳና ላይ ቅስቀሳው ቅዳሜ ህዳር 20, 2001 ዓ.ም በሁለቱም መኪኖቹ ያሉት አባላቱና መኪኖቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሲሆን በቂርቆስ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት የአንደኛው መኪና ቀስቃሾቹም ድብደባ የደረሰባቸው መሆኑን ከሥፍራው የደረሱ የፓርቲው አባላት ገልፀዋል፡፡
የምስራቅ አዲስ አበባ ቀጠና ቀስቃሾች ከጽ/ቤቱ ተነስተው በስታዲየም እየቀሰቀሱ ወደ ቂርቆስ አካባቢ በመንቀሳቀስ ላይ እንዳሉ ለገሃር አካባቢ በፖሊስ ተይዘው ወደ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡
በራሪ ወረቀቶቹን የበተኑና የተቀበሉ ሰዎችም ከጉምሩክ በወጡ የፌደራል ፖሊስ ድብደባ እንደደረሰባቸውና አንዳንዶቹም አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው አካባቢው የነበሩ የዓይን እማኞች ወዲያውኑ ወደ ፓርቲው ጽ/ቤት በመደወል ገልፀዋል፡፡ በቂርቆስ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩትን የመኢአድ ቀስቃሾች በመኪና ለይ የሰቀሉትን አረንÕዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ፖሊሶች የህ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አይደለም ብለው አስወርደው የተቀበልዋቸው ሲሆን አረንÕዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለው በእጅ ላይ የሚደረግ ባንዲራቸውንም እያስወለቁ የቀሙዋቸው መሆኑን ታሳሪዎቹ ከስፍራው ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው የነበረው ህዝብ ፖሊስ ጣቢያውን ከቦ በማስቸገሩ የመኢአድ ባነሮችና መፈክሮችን ፖሊስ ከመኪናው ላይ ያነሱት መሆኑ ታውsል፡፡ ከቦ በመጠባበቅ ላይ የሚገኘውንም ህዝብ በፖሊስ ተባረዋል፡፡
ወደ ምዕራብ አዲስ አበባ ቀጠና የተንቀሳቀሰው መኪና ጉዞውን ወደ ኢዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ለማድረግ እንደተነሳ ብዙም ሳይሄድ ፒያሳ አካባቢ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሊውል ችሏል፡፡
ህዳር 18 ቀን 2001 ዓ.ም ቅስቀሳው በተጀመረ ወቅት የፖሊስ ሠራዊት በድምጽ መቀስቀስ አትችሉም ወረቀት በመበተንና በሙዚቃ ግን ይቻላል ሲል፣በህዳር 19 ቀን 2001 ዓ.ም ደግሞ የቴዲን ዘፈን ማሰማት አትችሉም ወረቀት መበተን ግን ፈቅደንላቸኋል ብለው ለተወሠነ ሰዓት የፓርቲውን አባሎች በቁጥጥር ስር አውለው መልቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ህዳር 20 ቀን 2001 ዓ.ም ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅስቀሳውን ማቆም አለባችሁ በማለት የመኢአድ አባሎች ከነመኪናቸው ታስረዋል፡፡
በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በነገሩ ጣልቃ በመግባት ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉት ሲሆን በሁኔታውም ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡ ከውጪ የሚገኙ የፓርቲ ደጋፊዎች የፖሊስ ኮሚሽን ባልደረባ ኢንስፔክተር ዘላለም ስለጉዳዩ ተጠይቀው ማንንም አላሰርንም ብለዋል፡፡
|