|
ወያኔ 463 ሚሊዮን በላይ ማፈሱ ተገለጠ |
|
|
|
Monday, 04 August 2008 |
|
የወያኔ ሥርዓተ-አገዛዝ ከ11 ድርጅቶች ሽያጭ ከብር 463 ሚሊዮን በላይ ማፈሱ ተገለጠ፡፡
የኢትዮጵያን ሕዝብ የፖለቲካ ሥልጣን በጠብመንጃ ኃይል ቀምቶ በብሔራዊ ኤኮኖሚያችን አዛዥና ናዛዥ የሆነው የወያኔ ሥርዓተ-አገዛዝ በቅርቡ ከ11 ድርጅቶች ሽያጭ ከብር 463 ሚሊዮን በላይ ማፈሱን አንድ ምስጢራዊ ሰነድ ሰሞኑን ገለጠ፡፡
እንደ ምሥጢራዊ ሰነዱ አገላለፅ ለሽያጭ ቀርበው የተቸበቸቡ ድርጅቶች 1. ድሬዳዋ ራስ ሆቴል ቁጥር አንድ 2 ድሬዳዋ ራስ ሆቴል ቁጥር ሁለት 3 ሐረር ራስ ሆቴል 4. ባሌ ጎባ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል 5. ኮልፌ የቤት ዕቃዎች ፋብሪካ 6. ዐባይ የቴክኒክና ንግድ አክስዮን ማህበር 7. አልኪን ሪዝን አክስዮን ማህበር 8.ኢካፊኮ አክሲዮን ማህበር 9. የኢትዮጵያ ብረታ ብረት ፋብሪካ 1ዐ. አቃቂ ብረታብረት ፋብሪካ እና 11. የኢትዮጵያ ቅመማ ቅመም ፋብሪካ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከእነዚህ ሌላ 18 ድርጅቶች ለሽያጭ ቀርበው ገዥ አጥተው መቆማቸውን ምስጢራዊ ሰነዱ ይፋ አድርጓል፡፡
በጠቅላላው በ11 ድርጅቶች ሽያጭ የወያኔ ሥርዓተ-አገዛዝ ብር 463671965.2 መሰብሰቡ ታውቋል፡፡
|