|
ኢሳያስ አፈወርቂ 86 አባሎች ያቀፈ “ሓይሊ -ዕማም” ... |
|
|
|
Thursday, 26 June 2008 |
|
Any Eritrean
tried to cross border faces immediate execution
ኢሳያስ አፈወርቂ 86 አባሎች
ያቀፈ “ሓይሊ -ዕማም” (ተልእኮ) በመባል የተሰየመ አዲስ የነብሰ-ገዳዮች ወታደራዊ ጓድ ማደራጀቱን ታወቀ።
አገር
ጥለዉ ለመኮብለል ሲሞክሩ ድምበር ላይ የሚያዙት የኤርትራ ወጣቶች ፍርሃት ዉስጥ የከተተተዉ “ሓይሊ-ዕማም” የተባለዉ በኢሳያስ አፈወርቂ የሚታዘዘዉ አዲስ የነብሰ-ገዳይ ልዩ ስኳድ ከሁለት ሳምንት በፊት
(በፈረንጅ አቆጠጠር ጁን 16- 2008) አምስት የኤርትራ ወጣቶች ድምበር ተሻግረዉ ወደ ሱዳን ለመኮብለል ሲሞክሩ ተይዘዉ በቅጸበት ወደዚሁ ልዩ ስኳድ ዘንድ ተወስደዉ የተረሸኑ መሆናቸዉንና፤ “አስማሪኖ.ካም” የተባለዉ የኤርትራዊያን የህዋ-ሰሌዳ (ኢንተርኔት) ገለጸ።
ከላይ በተጠቀሰዉ ቀን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከጥዋቱ በ5፡00
ሰዓት አካባቢ፡ አምስቱ ወጣት ኤርትራዊያን ወደ ሱዳን ለመኮብለል
እተሻገሩ እንዳሉ “ግርማይካ” በተባለዉ አካባቢ ከተያዙ ከሰባትት ሰዓት ቆይታ በሗላ “ሞስዳፕ” በተባለ ቦታ ተረሽነዋል።
ይህ “ሓይሊ ዕማም” የተባለዉ ልዩ ጓድ ከኢሳያስ ጋር በቀጥታ ከአስመራ
ልዩ ግንኙነት አለዉ።። ይህ ቡድን 86 አባላት አቅፎ በሦስት ንኡስ ክፍል የተከፈለ ነዉ። ከእንግዲህ ወዲህ ማንኛዉም ሰዉ አገር
ጥሎ ለመኮብለል ከተያዘ ወደ እዚህኛዉ ልዩ የረሻኝ ቡድን ተልኮ ቅጽበታዊ እርምጃ ስለሚወሰድበት ወላጆች በፍርሃት ተዉጠዋል።/-/
ጌታቸዉ ረዳ
|