|
ለትግሬዎቹ “ባዳ“ ለኤርትራዎቹ ግን ቤት “ለእንግዳ” |
|
|
|
Monday, 30 June 2008 |
|
ኢትዮጵያ ለትግሬዎቹ “ባዳ“ ለኤርትራዎቹ ግን ቤት “ለእንግዳ”
( ጌታቸዉ ረዳ)
(ሳን ሆዘ -ካሊፎርኒያ)
ዛሬስ ዕረፍት ልዉሰድና እስቲ አዕምሮየን እረፍት ልስጠዉ እልና፤ በጎን፤ ሌላ ዕረፍት የ ማይሰጠን ጉድ በየደቂቃዉ ከዚህም ከዚያም እየጎረፈ አላሳርፍ ሲለኝና ወደ መከረኛዎቹ ወደ እናንተዉ ለመጮህ ሚድያ ዉስጥ እገባለሁ።
ለነገሩ ዛሬ ይህ ዜና ስጽፍ እሁድ ነዉና በፈጣሪ ትዛዝ ማረፍ ነበረብኝ። በደምቡ መሰረት ማለት ነዉ። ወያኔዎቹ ሚድያና ተቃዋሚ ነን ከሚሉት ሜዲያዎቹ አንዳነዶቹን ልጎብኝና እስኪ እንደሰዉ አንድ ቀንም ቢሆን ከማንምበብ ልረፍ ብየ ነበር። አልሆነም።
|