|
”የህወሐት ታጋዮች በሰባት ጥይት ድብድበዉ ጫካ ወስደዉ ጣሉኝ |
|
|
|
Saturday, 13 September 2008 |
|
የትግራይ ድያቆናትንና የቀሳዉስት ዕምባ
(ለማስታወሻዎ)
የህወሐት ታጋዮች በሰባት ጥይት ድብድበዉ ጫካ ወስደዉ ጣሉኝ”
(ምንጭ፦ ኢትኦጵ መጽሄት- ቅጽ 2 ቁጥር 016 መስከረም 1993 ዓ.ም)
( ጌታቸዉ ረዳ)
( ሳን ሆዘ ካሊፎርኒያ )
ይህ ታሪክ ኣማርኛ ለማያነቡ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተርጉሜ መሳ ለመሳ ሰሞኑን በዚህ የህዋ ሰሌዳ ቀርቧል። ሃቅን አድበስብሶ ለጊዜዉ በመሸፋፈን ዜጎችን ያስለቀሱ ወንጀለኞችን ባንዳንድ አድረባዮችና ጅላጅል ተቃዋሚዎች ሽፋን ሰጪነት፤የህወሐት አመራር ወንጀለኞች የህዝብ ኣሳቢዎች እንደነበሩና ዛሬም ነጻ ያወጡናል ብለዉ በየራድዮናቸዉና በህዋ-ሰሌዳቸዉ አጉል ቅስቀሳ ሲያደርጉላቸዉ ብንታዘብም ፡ እዉነት ተሸፋፍኖ አይቀርምና፤ ሰሚ አጥተዉ ፤ የሚጮህላቸዉ ዜጋ ፍለጋ ለዓመታት የደም ዕምባ ላፈሰሱት የወያኔ አመራር ሰለባዎች ደግሞ በኛ በኩል በዚህ ዓምድ ዕምባቸዉና እሮሮአቸዉ ለሕዝብ እናስተጋባለን። ፈራጁ ታሪክ እና በዓይን የሚታይ ጥቃት እንጂ “ዘመን የለገሳቸዉ ግራ ተጋብተዉ የዋሁን ማህበረ ሰብ ግራ የሚያጋቡ አፈጮሌ ባለ ራዲዮኖችና የህዋ -ሰሌዳ ባለቤቶች ” አይደሉም።
|